ኤችአይቪ እንዲመረመሩ የሚመከሩባቸው ዝርዝር የህክምና ሁኔታዎች: - እንደ እርግዝና ፣ የአባላዘር በሽታ፣ የቫይራል ጉበት በሽታ(ሄፓታይተስ) ፣ ክብደት መቀነስ እና ሌሎች የሕክምና ሁኔታዎች ናቸው። 

በእስራኤል ሀገር የበሽታው ስርጭት ከጠቅላላው የህዝቡ ቁጥር 0.1% ያህል ነው ፣ ምንም እንኳን ምርመራ ማድረጉ ርካሽ ቢሆንም እና ምርመራው ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል እንዲሸፍን የሚመክሩ ሀገሮች ቢኖሩም በእስራኤል ሀገር ውስጥ ሁሉንም ህዝብ ለመመረመር እስከ አሁን ምንም አይነት የተሰጠ ምክር የለም:: 

አይችሉም፣ ኤች አይ ቪ በእስራኤል ሀገር ውስጥ በሁሉም የዕድሜ ክልል በሚገኙ የማንኛውም የማህበረሰብ ክፍሎች ተሰራጭቶ ይገኛል ፡፡  

ሐኪሙዎ ምርመራውን እንዲያደርጉ ለመምከር በቂ ምክንያት ስላላገኙ ሊሆን ይችላል ፣ ወይም ደግሞ በጊዜ እጥረት ምክንያት እርስዎ ስለማያውቁት በሽታ ከማነጋገር ይልቅ ወደዚህ ጣቢያ አስተላልፎዎታል ፡፡ 

ምርመራውን ያለክፍያ በቤተሰብ ሀኪምዎ በኩል በሁሉም ኩፖት ሆሊም ወይም በሆስፒታሎች በሚገኙ በማንኛውም የኤድስ ማእከላት - ራምባም (ሃይፋ) ፣ ሂላል ያፌ (ሀደራ) ፣ ሜየር (ክፋር ሳባ) ፣ ቴል ሃሾመር ፣ ኤኽሎቭ (ቴል አቪቭ) ፣ ካፕላን (ሬሆቮት) ፣ ሶሮካ (ቤርሸቫ) ፣ ሃዳሳህ (ኢየሩሳሌም) ማድረግ ይችላሉ: በሀዳሳ ኤ.ኬ. - በእየለቱ ሰኞ ከጥዋቱ 8:30 - 10:30 በተላላፊ በሽታዎች ክሊኒክ ፣ 6ኛ ፎቅ ላይ ምርመራዎች ይከናወናሉ - መታወቂያ ካርድ እና የኩፓት ሆሊም አባልነት ካርድ በቂ ነው: በተጨማሪም በእየለቱ እሁድ ከቀኑ 17: 00 - 20: 00 በኢየሩሳሌም መርካዝ ሓኢር ፣ ባይት-ፓቱዋህ፣ሽሙኤል ሃናጊድ 1 ፣ 4 ኛ ፎቅ ምርመራ ማድረግ ይቻላል: ቴል አቪቭ - ቫአድ ለሚልሀማ በኤድስ- ሃናጺቭ ጎዳና 18 ፣ ቴል አቪቭ ፣ 1 ኛ ፎቅ ፣ በየእለቱ እሁድ፣ ማክሰኞ፣ ሮቡዑ፣ ሐሙስና አርብ ምርመራ ማድረግ ይቻላል ፡፡  

ቢያንስ 3 ሳምንታት ፡፡ 

ምርመራው መቼና የት እንደተደረገ መሰረትን ያደረገ ነው ፥ ምርመራው በሀዳሳ ከተደረገ በሁለት ቀናት ውስጥ መልስ ለማግኘት ይችላሉ ፥አስቸኳይ ከሆነ ምርመራው በተደረገበት ዕለት መልስ ማግኘት ይችላሉ ፡፡